በግንባታ ላይ የሚገኘው የባህር ዳር ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተርሚናል በጥቂት ወራት ውስጥ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተባለ

ሰብስክራይብ

በግንባታ ላይ የሚገኘው የባህር ዳር ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተርሚናል በጥቂት ወራት ውስጥ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተባለ

ተርሚናሉን ሙሉ ለሙሉ አጠናቆ ወደ ሥራ ለማስገባት የሚያስችሉ ቀሪ የግንባታ ሂደቶች በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡

የከተማዋን የትራንስፖርት ትስስር ለማጠናከር፣ የጎብኚዎችን ምቾት ለመጨመር እና የቱሪዝም እንዲሁም የኢኮኖሚ ግቦችን ለማሳካት ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግም ተጠቁሟል።

“ተርሚናሉ ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ፣ የተሳፋሪዎችን ምቾት ከግምት ውስጥ ባስገባ እና ማራኪ በሆነ መልኩ እየተገነባ ነው” ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በስፍራው ባደረጉት ጉብኝት ወቅት ተናግረዋል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0