የናይጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለጸረ-ሽብር ውይይት ቱርክን እንደሚጎበኙ ተገለጸ
20:04 25.01.2026 (የተሻሻለ: 20:14 25.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የናይጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለጸረ-ሽብር ውይይት ቱርክን እንደሚጎበኙ ተገለጸ
"ይህ ጉብኝት የናይጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዩሱፍ ማይታማ ቱጋር ወደ ቱርክ የሚያደርጉት የመጀመሪያው ይፋዊ ጉብኝት ይሆናል" ሲሉ የቱርክ ዲፕሎማሲያዊ ምንጮች ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
እንደ ምንጮቹ ገለጻ፤ የውይይቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች፦
🟠 ወታደራዊ እና የመከላከያ ትብብር፦ ሁለቱም ወገኖች ይህ ዘርፍ ከፍተኛ የመጠናከር አቅም እንዳለው ያምናሉ። በሽብርተኝነት ላይ የሚደረገው የጋራ እርምጃ እና አንድነትን ማጠናከር የውይይቱ ዋነኛ ነጥብ ይሆናል።
🟠 የናይጄሪያ ቀጣናዊ ሚና እና የሁለትዮሽ ግንኙነት፦ ናይጄሪያ በምዕራብ አፍሪካ መረጋጋት፣ ሰላም እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ላይ ስላላት ሚና እንዲሁም የሁለትዮሽ ንግድ እና ኢንቨስትመንትን ማሳደግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ይመክራሉ።
🟠 የጋዛ ቀውስ፦ ሁለቱም ወገኖች የእስልምና ትብብር ድርጅት እና የአረብ ሊግ ጥምር ቡድን የተኩስ አቁሙ እንዲቀጥል፣ ሰብዓዊ ሁኔታዎች እንዲሻሻሉ እና የሁለት-ሀገር መፍትሔ እንዲረጋገጥ የሚያደርጉትን ጥረት እንደሚደግፉ ይጠበቃል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X