1,050 የባትሪ መሙያ ጣቢያዎች ከአዲስ አበባ ውጪ እንደሚገነቡ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ1,050 የባትሪ መሙያ ጣቢያዎች ከአዲስ አበባ ውጪ እንደሚገነቡ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ
1,050 የባትሪ መሙያ ጣቢያዎች ከአዲስ አበባ ውጪ እንደሚገነቡ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 25.01.2026
ሰብስክራይብ

1,050 የባትሪ መሙያ ጣቢያዎች  ከአዲስ አበባ ውጪ እንደሚገነቡ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ

በአጠቃላይ በመላ ሀገሪቱ ከ2,200 በላይ ፈጣን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያዎችን ለመገንባት እንደታቀደ ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

የባትሪ መሙያ ጣቢያዎችን እና የኃይል መሠረተ ልማት ችግሮችን ለመቅረፍ በኢትዮ-ጅቡቲ መስመር ደወሌ እና ጋላፊ አካባቢ ጭምር ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተቋሙን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።

"ከነዳጅ ወደ ታዳሽ ኃይል ለሚደረገው ጉዞ ከመሠረተ ልማት ማሟላት ባሻገር የኤሌክትሪክ መኪና አስመጪዎችን ለማበረታታት፣ ያሉባቸውን ችግሮችም ለመፍታት በገንዘብም ጭምር ድጋፍ እናደርግላቸዋለን" ሲሉ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን ተናግረዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0