ናይጄሪያ የመጀመሪያውን ብሔራዊ የቅርንፉድ እርሻ ፕሮግራም ይፋ አደረገች

ናይጄሪያ የመጀመሪያውን ብሔራዊ የቅርንፉድ እርሻ ፕሮግራም ይፋ አደረገች
የናይጄሪያ የቅርንፉድ አምራቾች፣ አቀነባባሪዎች እና ነጋዴዎች ማኅበር እንደገለጸው፤ ይህ ሀገር አቀፍ ፕሮግራም ከ74 ሺህ በላይ ገበሬዎችን የሚያሳትፍ ሲሆን፣ ናይጄሪያን ከታንዛኒያ ቀጥላ በአፍሪካ ሁለተኛዋ የቅርንፉድ አምራች ሀገር ለማድረግ ያለመ ነው።
የፕሮግራሙ ዋና ዋና ዝርዝሮች፦
ተደራሽነት፦ በእያንዳንዱ የናይጄሪያ 36 ግዛቶች ውስጥ ቢያንስ 2 ሺህ ገበሬዎች በሙከራ ፕሮግራሙ ላይ ይሳተፋሉ። ለእያንዳንዱ ገበሬ ግማሽ ሄክታር መሬት ለማልማት የሚያስችል ጥራት ያለው ዘር እና ሌሎች ግብዓቶች ይቀርባሉ።
ግብ፦ በምግብ እና በመድኃኒት ኢንዱስትሪዎች ያለውን ከፍተኛ የሀገር ውስጥ እና የዓለም አቀፍ ፍላጎት መጠቀም እንዲሁም ናይጄሪያን ከቅርንፉድ አስመጪነት ወደ ላኪነት ማሸጋገር።
የሚጠበቀው ውጤት፦ ፕሮግራሙ ለሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ግኝት እና ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ ጨዋታ ቀያሪ ነው ተብሏል። በተጨማሪም የሌሎች ሰብሎች ዋጋ በሚቀንስበት ወቅት ገበሬዎችን ከኪሳራ የሚታደግ ይሆናል።
ድጋፍ፦ ለፕሮግራሙ የሚሆኑ የተሻሻሉ ዘሮች ከታንዛኒያ የተገኙ ሲሆን፣ አጠቃላይ የአመራረት ሥልጠና መመሪያ ደግሞ በናይጄሪያው አህመዱ ቤሎ ዩኒቨርሲቲ ተዘጋጅቷል።
ይህ ተነሳሽነት ድህነትን ለመቀነስ፣ የሥራ ዕድል ለመፍጠር እና ሴት ገበሬዎችን ለማብቃት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑንና ለገጠር ኢኮኖሚ ዕድገት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ማኅበሩ አፅንኦት ሰጥቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X