ጅግጅጋ ከተማ የፕላስቲክ ከረጢቶችን መጠቀም ሙሉ በሙሉ አቆመች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱጅግጅጋ ከተማ የፕላስቲክ ከረጢቶችን መጠቀም ሙሉ በሙሉ አቆመች
ጅግጅጋ ከተማ የፕላስቲክ ከረጢቶችን መጠቀም ሙሉ በሙሉ አቆመች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 25.01.2026
ሰብስክራይብ

ጅግጅጋ ከተማ የፕላስቲክ ከረጢቶችን መጠቀም ሙሉ በሙሉ አቆመች

የሶማሌ ክልል መዲና የፕላስቲክ ከረጢቶችን ሙሉ በሙሉ በማስቀረት በወረቀትና በጨርቅ በተሠሩ ተኪ ምርቶች አገልግሎት እንዳስጀመረች ተሰማቷል፡፡

ውሳኔው በሀገር አቀፍ ደረጃ የፕላስቲክ ብክለትን ለመከላከል የተያዘውን አቅጣጫ መነሻ ያደረገ መሆኑን የሶማሌ ክልል የአካባቢ ጥበቃና ገጠር መሬት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሙሄዲን አብዲ ሁሴን (ኢ/ር) አስታውቀዋል።

የፕላስቲክ ፌስታሎችን ከአገልግሎት የማስወገድ ሥራው በቀጣይም በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ተግባራዊ እንደሚደረግ መናገራቸውን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።

በክልሉ የፕላስቲክ ማሸጊያዎችን የሚተኩ ምርቶችን የሚያመርቱ ፋብሪካዎችን ለመገንባት መታቀዱን የገለጹት ኃላፊው፤ ባለሀብቶችና ኢንቨስተሮች በዘርፉ እንዲሰማሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0