ብሪታንያ በአሜሪካ ጫና የቻጎስ ደሴቶች ረቂቅ ሕግን በመሠረዝ ቁልፍ የአፍሪካ ሀገር የሉዓላዊነት ጥያቄ እንዲራዘም አድርጋለች - ዘገባ

ብሪታንያ በአሜሪካ ጫና የቻጎስ ደሴቶች ረቂቅ ሕግን በመሠረዝ ቁልፍ የአፍሪካ ሀገር የሉዓላዊነት ጥያቄ እንዲራዘም አድርጋለች - ዘገባ
የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኪር ስታርመር፤ ፕሬዚዳንት ትራምፕ የቻጎስ ደሴቶችን ለመመለስ የተደረሰውን ስምምነት "ታላቅ ሞኝነት" በማለት አሜሪካ ቀደም ሲል የሰጠችውን ድጋፍ በድንገት እንድትቀለብስ በማድረጋቸው፤ ሕጉን እንዳነሱ የብሪታንያ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ሉዓላዊነት እና ደህንነት
⏺ ረቂቅ ሕጉ የዲዬጎ ጋርሺያ የጦር ሠፈርን ጨምሮ በደሴቶቹ ላይ ያላትን ሉዓላዊነት ከሚደግፉ በርካታ ዓለም አቀፍ የፍርድ ቤት ውሳኔዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ ለሞሪሸስ ለማስተላለፍ ያለመ ነበር።
⏺ ዩናይትድ ኪንግደም እና አሜሪካ
ቀልፍ የሆነውን ስትራቴጂካዊ የጋራ የጦር ሠፈር ከሞሪሸስ በኪራይ መልሶ መጠቀም በሚያስችል ስምምነት የረጅም ጊዜ ይዞታን ማረጋገጥ አስፈላጊ ነው ሲሉ ይከራከራሉ።
⏺ በብሪታንያ የሚገኙ የስምምነቱ ተቃዋሚዎች ግን ደሴቶቹን ማስረከብ እ.ኤ.አ በ1966 በአሜሪካና እና ብሪታንያ መካከል የተፈረመውን ስምምነት ይጥሳል በማለት ረቂቅ ሕጉ በፓርላማ እንዳይጸድቅ አዘግይተውታል።
የቻጎስ ደሴቶች ጉዳይ በአፍሪካ የመጨረሻው ያልተቋጨ ከቅኝ አገዛዝ የመላቀቅ ጥያቄ ተደርጎ ይወሰዳል። የአፍሪካ ኅብረት የሞሪሸስን ጥያቄ በጥብቅ የሚደግፍ ሲሆን የብሪታንያን አስተዳደር እንደ ቅኝ አገዛዝ አሻራና ሕዝብን የማፈናቀል ተግባር አድርጎ ይመለከተዋል።
የብሪታንያ ምንጮች ረቂቅ አዋጁ ዳግም ወደ ፓርላማ እንደሚመለስ ቢገልጹም ያለ አሜሪካ ድጋፍ ግን የወደፊት እጣ ፈንታው አጠራጣሪ መሆኑ ተነግሯል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X