ጊኒ ቢሳው አወዛጋቢውንና በአሜሪካ የገንዘብ ድጋፍ የሚካሄደው የክትባት ሙከራ መታገዱን አረጋጠች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱጊኒ ቢሳው አወዛጋቢውንና በአሜሪካ የገንዘብ ድጋፍ የሚካሄደው የክትባት ሙከራ መታገዱን አረጋጠች
ጊኒ ቢሳው አወዛጋቢውንና በአሜሪካ የገንዘብ ድጋፍ የሚካሄደው የክትባት ሙከራ መታገዱን አረጋጠች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 24.01.2026
ሰብስክራይብ

ጊኒ ቢሳው አወዛጋቢውንና በአሜሪካ የገንዘብ ድጋፍ የሚካሄደው የክትባት ሙከራ መታገዱን አረጋጠች

​ የጊኒ ቢሳው የጤና ሚኒስትር ኪንሂን ናንቶቴ፤ ውሳኔው የተላለፈው የሕክምና ሥነ-ምግባር ኮሚቴ በአሜሪካ የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግለት "የሄፓታይተስ ቢ" ክትባት ሙከራ ሳይንሳዊ ይዘት በትክክል አልተገመገመም ማለቱን ተከትሎ እንደሆነ ገልጸዋል።

​በክትባት ሙከራው ከ14 ሺህ አራስ ልጆች ለግማሾቹ የሚሰጠውን የሄፓታይተስ ቢ ክትባት ለማዘግየት ታቅዶ ነበር። ይህም ክትባቱ ወዲያውኑ መሰጠት አለበት ከሚለው የዓለም ጤና ድርጅት መመሪያ ጋር የተቃረነ ሲሆን ወደ 20 በመቶ የሚጠጉ አዋቂዎች በቫይረሱ በሚጠቁባት ሀገር ውስጥ የሥነ-ምግባር ስጋትን አስነስቷል።

​ መጀመሪያ ለጥናቱ ፍቃድ ሰጥቶ የነበረው የጊኒ የሥነ-ምግባር ኮሚቴ፤ ክትባቱን ለመከልከል ቁልፍ መረጃዎች በትክክል አልቀረቡም ብሏል። ማንኛውም የተሻሻለ የሙከራ እቅድ የመንግሥትን ሙሉ ፍቃድ ማግኘት እንደሚኖርበትም ኮሚቴው አመልክቷል።

​የአፍሪካ የበሽታ መከላከል እና መቆጣጠሪያ ማዕከል (አፍሪካ ሲዲሲ) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ ባለፈው ሳምንት "ይህ የሀገሪቱ የሉዓላዊነት ጉዳይ ነው" በማለት የጊኒ ቢሳውን ውሳኔ  ደግፈዋል።

​ ይህም ቀደም ሲል የክትባት ሙከራው ይቀጥላል ካሉት የአሜሪካ የጤና ባለሥልጣናት ጋር ይቃረናል።

​አፍሪካ ሲዲሲ የጥናቱን ይዘት በመገምገም ረገድ ለጊኒ ቢሳው ድጋፍ እንደሚያደርግ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0