በዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም የሚደገፈው የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ላይ ከ407 ቢሊዮን ብር በላይ ኪሳራ አስከተለ
19:03 24.01.2026 (የተሻሻለ: 19:04 24.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም የሚደገፈው የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ላይ ከ407 ቢሊዮን ብር በላይ ኪሳራ አስከተለ
በ2017 የበጀት ዓመት መጨረሻ ለተመዘገበው ኪሳራ ዋነኛ መንስኤ የውጭ ምንዛሬ ተመን ማስተካከያውን ተከትሎ የውጭ ምንዛሬ ሀብቶችና ዕዳዎች በድጋሚ በመገመታቸው እንደሆነ የባንኩ የኦዲት ሪፖርት ይፋ አድርጓል ሲል ሚዲያ ዘግቧል።
የውጭ ምንዛሬ ኪሳራው በ2016 የበጀት ዓመት ከነበረበት 38.13 ቢሊዮን ብር በከፍተኛ ሁኔታ ወደ 445.23 ቢሊዮን ብር አሻቅቧል።
ይህ ከፍተኛ ጭማሪ የብሔራዊ ባንክን አጠቃላይ የሥራ ማስኬጃ ኪሳራ በ2016 የበጀት ዓመት ከነበረበት 10.51 ቢሊዮን ብር ወደ 428.56 ቢሊዮን ብር ከፍ እንዲል አድርጎታል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከወርቅ ሽያጭ እና የወርቅ ክምችት ዋጋ ቅነሳም 57.2 ቢሊዮን ብር ኪሳራ መዝግቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X