የአቡ ዳቢ የዩክሬን ድርድር ባልተቋጩ የአሜሪካ የሰላም ዕቅድ ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር - የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
18:18 24.01.2026 (የተሻሻለ: 18:24 24.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአቡ ዳቢ የዩክሬን ድርድር ባልተቋጩ የአሜሪካ የሰላም ዕቅድ ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር - የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
ስፑትኒክ ያገኘው የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ ዋና ዋና ነጥቦች፦
▪ የሩሲያ እና የዩክሬን ልዑካን በአቡ ዳቢ ከአሜሪካ ጋር በተደረገው የሦስትዮሽ ውይይት ከዚህ በፊት በተለየ ቀጥተኛ ግንኙነት አድርገዋል።
▪ ለሁለት ቀናት የቆየው ድርድር “በገንቢ እና አዎንታዊ መንፈስ” ተካሂዷል።
▪ ውይይቶቹ ትኩረታቸውን ያደረጉት አሜሪካ ባቀረበችው የሰላም ማዕቀፍ እልባት ባላገኙ ነጥቦች ላይ እና ሁሉን አቀፍ ስምምነት ላይ ለመድረስ በሚያግዙ የጋራ መተማመኛ እርምጃዎች ላይ ነው።
▪ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ግጭቶች ያለ ውይይት ሊፈቱ እንደማይችሉ አጽንኦት በመስጠት ለዓለም አቀፍ የግጭት አፈታት ጥረቶች የምታደርገውን ድጋፍ እንደምትቀጥል ቃል ገብታለች።
▪ዶናልድ ትራምፕ ድርድሩ እንዲመቻች ላደረጉት ሚና አድናቆቷን ገልጻለች።
ስብሰባዎቹ አዲስ በተቋቋመው የሩሲያ-አሜሪካ-ዩክሬን የሦስትዮሽ የደህንነት ጉዳዮች የሥራ ቡድን የተካሄው የመጀመሪያው ነው። ቡድኑ በአድሚራል ኢጎር ኮስቲዩኮቭ የሚመሩ ከፍተኛ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ባለሥልጣናትን አካቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X