ተመራማሪው “የአረቢካ ቡና" የሚለው ስያሜ “የኢትዮጵያ ቡና” ተብሎ እንዲቀየር ምክረ ሃሳብ አቀረቡ
18:03 24.01.2026 (የተሻሻለ: 22:54 24.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ተመራማሪው “የአረቢካ ቡና" የሚለው ስያሜ “የኢትዮጵያ ቡና” ተብሎ እንዲቀየር ምክረ ሃሳብ አቀረቡ
ኢትዮጵያ የቡና መገኛ በመሆኗ ለታሪክና ለሳይንሳዊ አስተዋፅኦ እውቅና ለመስጠት የስያሜ ለውጥ እንዲደረግ ተመራማሪው ሰሎሞን ተክሌ ጥሪ አቅርበዋል።
መገኛው ኢትዮጵያ የሆነው “አረቢካ ቡና” እውነተኛ ምንጩን የሚያንፀባርቅ ስያሜ ያስፈልገዋል ብለዋል።
በሌላ በኩል ሌሎች ሀገራት የቡና መገኛ ነን በማለት የሚያቀርቡትን መረጃ አልባ መከራከሪያ ነቅፈዋል።
ተመራማሪው በተጨማሪም የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት እና ባለድርሻ አካላት ኢትዮጵያ የቡና መገኛ መሆኗን በሳይንሳዊ መንገድ በማረጋገጥ በዩኔስኮ እውቅና ለማስገኘት እንዲሠሩ አሳስበዋል።
"ታሪካዊ እና ሳይንሳዊ ምንጮች ቡና ከኢትዮጵያ የተገኘ መሆኑን በግልጽ ያሳያሉ" ሲሉ ተመራማሪው ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X