የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከ400ሺህ በላይ መጽሐፍትን በዲጂታል ሥርዓት እንዳደራጀ አስታወቀ
16:42 24.01.2026 (የተሻሻለ: 20:54 24.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከ400ሺህ በላይ መጽሐፍትን በዲጂታል ሥርዓት እንዳደራጀ አስታወቀ
የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት አሥራት አፀደወይን፤ ተቁሙ የዲጂታል ቤተ-መጽሐፍት በማቋቋምና ጥናታዊ ጽሁፎችና የተለያዩ መጽሐፍትን በዲጂታል ሥርዓት በማደራጀት አንባቢ ትውልድ አንዲፈጠር የድርሻውን እየተወጣ ነው ብለዋል።
ከዚህ አኳያ ዩኒቨርሲቲው የዲጂታል ቤተ-መጽሐፍት በማቋቋም ከ400 ሺህ በላይ የታሪክ፣ የሳይንስና የምርምር መጽሐፍትን ጨምሮ ከ10 ሺህ በላይ ጥናታዊ ጽሁፎችን በዲጂታል ሥርዓት እንዳደራጀ ገልጸዋል።
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ''መጽሐፍት ለንባብ፣ ንባብ ለዕውቀት፣ ዕውቀት ለህይወት'' በሚል መሪ ሃሳብ በየዓመቱ የሚያዘጋጀውን የመጽሐፍት ዐውደ ርዕይ ከፍቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X