ናሚቢያ የኃይል እጥረቷን በዘላቂነት ለመፍታት የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ለማቋቋም እያጤነች መሆኑን የሀገሪቱ ባለሥልጣን ገለጹ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱናሚቢያ የኃይል እጥረቷን በዘላቂነት ለመፍታት የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ለማቋቋም እያጤነች መሆኑን የሀገሪቱ ባለሥልጣን ገለጹ
ናሚቢያ የኃይል እጥረቷን በዘላቂነት ለመፍታት የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ለማቋቋም እያጤነች መሆኑን የሀገሪቱ ባለሥልጣን ገለጹ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 24.01.2026
ሰብስክራይብ

ናሚቢያ የኃይል እጥረቷን በዘላቂነት ለመፍታት የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ለማቋቋም እያጤነች መሆኑን የሀገሪቱ ባለሥልጣን ገለጹ

"በአፍሪካ ግዙፍ ከዓለም ደግሞ ሦስተኛ የዩራኒየም አምራች እንደመሆናችን መጠን፤ በተለይም ጥሬ ዕቃዎቻችን በዓለም ዙሪያ ለኒውክሌር ማመንጫዎች ኃይል እየሆኑ ባለበት ሁኔታ እኛ ከኒውኩሌር ኃይል ልማት ወደ ኋላ ማለት አንችልም" ሲሉ የብሔራዊ ፕላን ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ካይሬ ምቡዌንዴ በዳቮስ ፎረም ላይ ተናግረዋል።

ለዚህም መንግሥት ብሔራዊ የኒውክሌር ስትራቴጂ ማዘጋጀቱን የገለጹት ዳይሬክተሩ፤ በአሁኑ ወቅት ሀገሪቱ 60 በመቶ የሚሆነውን ኃይል ከደቡብ አፍሪካ እንደምታስገባና 60 በመቶ በታች የሚሆነው ሕዝቧ ብቻ የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት እንደሚያገኝ አክለዋል።

በተመሳሳይ የአነስተኛ ሞዱላር ሬአክተሮችን (አነስተኛ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫዎችን) መጠቀም እየተጤነ ሲሆን በዚህ ዘርፍ ልምድ ካላቸው ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር የልምድ ልውውጥ ለማድረግ መታቀዱን ጠቁመዋል።

ናሚቢያ እና ሩሲያ የዩራኒየም ማዕድን ክምችን በተመለከተ በጋራ ለመሥራት ጥር 6 ቀን መወያየታቸውን የሩሲያ የኒውክሌር ኮርፖሬሽ ሮሳቶም ማስታወቁ ይታወሳል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0