አፍሪካን በጤና ፈጠራ ስራዎች ችላ ማለት ለዓለም አቀፍ ደህንነት ስጋት የሚሆነው ለምንድን ነው? - የዓለም ንግድ ድርጅት መሪ በዳቮስ ማብራሪያ ሰጡ

ሰብስክራይብ

አፍሪካን በጤና ፈጠራ ስራዎች ችላ ማለት ለዓለም አቀፍ ደህንነት ስጋት የሚሆነው ለምንድን ነው? - የዓለም ንግድ ድርጅት መሪ በዳቮስ ማብራሪያ ሰጡ

በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ፣ በአውሮፓ ኅብረት እና በቻይና ላይ ያተኮረው የመድኃኒት እና የባዮቴክኖሎጂ ፈጠራ እድገት፣ እጅግ በሚያስደንቅ ሁኔታ ትኩረቱን ያደረገው በዕድሜ በገፉና ከፍተኛ ገቢ ባላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ መሆኑን በመጥቀስ  የዓለም ንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ንጎዚ ኦኮንጆ-ኢዊላ በዳቮስ በተካሄደው የዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም ላይ አስጠንቅቀዋል።

እንደ እሳቸው ገለጻ፣ የአፍሪካን እና የሌሎች የደቡባዊው ዓለም አካባቢዎችን የጤና ፍላጎቶች ችላ ማለት ኢ-ፍትሃዊ ብቻ ሳይሆን አደገኛም ነው።

ኦኮንጆ-ኢዊላ፣ “የቀረውን ዓለም ችላ ካልን፣ እዚያ የሚከሰተው ነገር ተመልሶ እኛኑ ሊጎዳን እንደሚችል አናውቅም” ሲሉ ዓለም አቀፍ የጤና ልዩነቶችን ከወደፊት የደህንነት ስጋቶች ጋር በማያያዝ አስጠንቅቀዋል።

ዋና ዳይሬክተሯ፣ የአፍሪካን የሕዝብ ቁጥር እድገት ትንበያም አጋርተዋል። እ.ኤ.አ. በ2050 አፍሪካ 2.5 ቢሊዮን ሕዝብ ይኖራታል፤ ከዚህ ውስጥ 800 ሚሊዮኑ መካከለኛ ገቢ የሚኖራቸው ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚገኙ አራት ሠራተኞች መካከል አንዱ አፍሪካዊ ይሆናል። “እነሱ የነገው የዓለም ገበያዎች ናቸው” በማለት ለተሰብሳቢዎቹ አስታውሰዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0