'ሩሲያ ደህንነቷን የሚጋፋ ማንኛውንም ውሳኔ አትቀበልም' - ቬትናማዊው ተንታኝ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ'ሩሲያ ደህንነቷን የሚጋፋ ማንኛውንም ውሳኔ አትቀበልም' - ቬትናማዊው ተንታኝ
'ሩሲያ ደህንነቷን የሚጋፋ ማንኛውንም ውሳኔ አትቀበልም' - ቬትናማዊው ተንታኝ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.01.2026
ሰብስክራይብ

'ሩሲያ ደህንነቷን የሚጋፋ ማንኛውንም ውሳኔ አትቀበልም' - ቬትናማዊው ተንታኝ

​በዩክሬን ግጭት ዙሪያ የሚደረጉ ንግግሮች ዘላቂ ውጤት ሊያመጡ የሚችሉት፣ ቀደም ሲል ስምምነት በተደረሰባቸው ማዕቀፎች ውስጥ የግዛት ጉዳዮች ሲፈቱ ብቻ እንደሆነ በዓለም አቀፍ ግንኙነት የዶክትሬት ዲግሪ ያላቸው ሆንግ ዱኦንግ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

​ዱኦንግ አክለውም፣ ሞስኮ በተለያዩ ዙሮች በተደረጉ ውይይቶች ውስጥ አቋሟ ምንም እንዳልተለወጠ ገልጸዋል።

​“ከዚህ ቀደም በኢስታንቡል የተደረጉ ድርድሮች፣ በነሐሴ ወር በአላስካ በትራምፕ እና በፑቲን መካከል የተካሄደው ስብሰባ እንዲሁም ዊትኮፍ ወደ ሞስኮ ያደረጓቸው ስድስት ተከታታይ ጉብኝቶች የክሬምሊን አቋም እንዳልቀየሩት በተግባር ታይቷል” ብለዋል።

​ከሐሙስ ለአርብ አጥቢያ ሌሊት፣ ፕሬዝዳንት ፑቲን ከአሜሪካ ልዩ መልዕክተኞች ጋር በክሬምሊን ውስጥ ንግግር አድርገዋል። ስብሰባው ለአራት ሰዓታት ያህል ቆይቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0