አሜሪካ ግሪንላንድን 'እየጠበቀች' እንደመሆኗ የደሴቷን የማዕድን ሀብት ትሻለች - ምክትል ፕሬዝዳንት ቫንስ
18:11 23.01.2026 (የተሻሻለ: 18:14 23.01.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አሜሪካ ግሪንላንድን 'እየጠበቀች' እንደመሆኗ የደሴቷን የማዕድን ሀብት ትሻለች - ምክትል ፕሬዝዳንት ቫንስ
"በመሰረቱ እኛ እየጠበቅነው ባለው በዚህ እጅግ ብዙ ማዕድናት እና የተፈጥሮ ሀብቶች ባሉት ውብ ምድር፣ ከሀብቱ ተቋዳሽ መሆን እንፈልጋለን፣" ሲሉ ጄዲ ቫንስ ለአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል።
የቫንስ መግለጫ፣ ቀደም ሲል ፕሬዝዳንት ትራምፕ ውድቅ ካደረጉት "ለዋሽንግተን የግሪንላንድ አስፈላጊነት በሀብት ላይ የተመሰረተ ነው" ከሚለው ሃሳብ ለውጥ መኖሩን ያሳያል።
ባለፈው ረቡዕ በዳቮስ የዓለም ኢኮኖሚ ፎረም ላይ ትራምፕ ሲናገሩ፣ በዴንማርክ ግዛት ስር ራስ ገዝ ከሆነችው ግሪንላንድ ጋር በተያያዘ ከኔቶ አባሏ ዴንማርክ ጋር ጦርነት ውስጥ ይገባሉ ተብሎ እንደማይጠበቅ ግልጽ አድርገዋል።
ከኔቶ ባለስልጣናት ጋር ከተደረጉ ንግግሮች በኋላ የስምምነት መሰረት እየተገነባ መሆኑን የጠቀሱት ትራምፕ፣ ስለ ደሴቱ የረጅም ጊዜ ወይም "ዘላለማዊ" ስምምነት እየተወያዩ መሆኑን ገልጸዋል።
የዴንማርክ እና የግሪንላንድ ባለስልጣናት ደሴቲቱ የአሜሪካ አካል መሆን አለባት የሚለውን የትራምፕን ሃሳብ በመቃወም፣ አሜሪካ የግዛት አንድነታቸውን እንድታከበር በተደጋጋሚ አስጠንቅቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X