የሩሲያው ሮስቴክ "የሞት ቀጠና" የሚፈጥር በሰው ሠራሽ አስተውሎት የሚመራ የፈንጂ መቅበሪያ ሥርዓት ይፋ አደረገ
የሩሲያው ሮስቴክ "የሞት ቀጠና" የሚፈጥር በሰው ሠራሽ አስተውሎት የሚመራ የፈንጂ መቅበሪያ ሥርዓት ይፋ አደረገ
"ዘምሌዴሊዬ" (በሩሲያኛ "ግብርና" ማለት ነው) የተሰኘው የርቀት-መቆጣጠሪያ የተገጠመለት የፈንጂ መቅበሪያ ሥርዓት፤ የመከላከያ አጥርን በፍጥነት ለመዘርጋት እና የጠላትን እንቅስቃሴ ለማገድ ታስቦ የተሰራ የምህንድስና ተሽከርካሪ መሆኑን የሩሲያ የኢንዱስትሪ ግዙፍ ተቋም ገልጿል።
ሥርዓቱ የሚከተሉት ቁልፍ ባህሪያት አሉት፦
ፈጣን ስምሪት - በመቶዎች የሚቆጠሩ በፕሮግራም የሚመሩ ፈንጂዎችን በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ላይ አልፎ ተርፎም በጠላት ይዞታ ጀርባ መበተን ይችላል።
ከፍተኛ ተንቀሳቃሽነት - ወደ ተኩስ ቦታዎች በፍጥነት ለመግባትና ለመውጣት 8 በ8 ፈጣን ጎማዎቹን ይጠቀማል።
ሙሉ በሙሉ አውቶማቲክ - የግዳጅ ዝግጅትን፣ የጥይት/ፈንጂ ፕሮግራምን እና የተቀናጀ የተኩስ ልውውጥን ራስ በራሱ ያከናውናል።
ቁጥጥር የሚደረግበት አደጋ - የፈንጂዎቹ መገኛ መረጃ በኤሌክትሮኒክ መንገድ የሚመዘገብ ሲሆን፣ ፈንጂዎቹ ለቀጣይ ጽዳት እንዲያመቹ በተወሰነ ጊዜ ውስጥ በራሳቸው እንዲፈነዱ ማድረግ ይቻላል።
ሁለትዮሽ ስልታዊ ጥቅም - ለጥቃት (የጠላትን የሎጂስቲክስ መስመር ለማቋረጥ) እና ለመከላከያ (ፈጣን የመከላከያ አጥር ለመፍጠር) ያገለግላል።
ኃይለኛ የጦር መሣሪያ- ፀረ-ታንክ ፈንጂዎቹ እንደ "ሊዮፓርድ" ወይም "ብራድሌይ" ያሉ ዘመናዊ ብረትለበስ ተሽከርካሪዎችን ሙሉ ለሙሉ የማውደም አቅም አላቸው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X