የሩሲያው ሮስቴክ "የሞት ቀጠና" የሚፈጥር በሰው ሠራሽ አስተውሎት የሚመራ የፈንጂ መቅበሪያ ሥርዓት ይፋ አደረገ

ሰብስክራይብ

የሩሲያው ሮስቴክ "የሞት ቀጠና" የሚፈጥር በሰው ሠራሽ አስተውሎት የሚመራ የፈንጂ መቅበሪያ ሥርዓት ይፋ አደረገ

​ "ዘምሌዴሊዬ" (በሩሲያኛ "ግብርና" ማለት ነው) የተሰኘው የርቀት-መቆጣጠሪያ የተገጠመለት የፈንጂ መቅበሪያ ሥርዓት፤ የመከላከያ አጥርን በፍጥነት ለመዘርጋት እና የጠላትን እንቅስቃሴ ለማገድ ታስቦ የተሰራ የምህንድስና ተሽከርካሪ መሆኑን የሩሲያ የኢንዱስትሪ ግዙፍ ተቋም ገልጿል።

ሥርዓቱ የሚከተሉት ቁልፍ ባህሪያት አሉት፦

ፈጣን ስምሪት - በመቶዎች የሚቆጠሩ በፕሮግራም የሚመሩ ፈንጂዎችን በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ላይ አልፎ ተርፎም በጠላት ይዞታ ጀርባ መበተን ይችላል።

ከፍተኛ ተንቀሳቃሽነት - ወደ ተኩስ ቦታዎች በፍጥነት ለመግባትና ለመውጣት 8 በ8 ፈጣን ጎማዎቹን  ይጠቀማል።

ሙሉ በሙሉ አውቶማቲክ - የግዳጅ ዝግጅትን፣ የጥይት/ፈንጂ ፕሮግራምን እና የተቀናጀ የተኩስ ልውውጥን ራስ በራሱ ያከናውናል።

ቁጥጥር የሚደረግበት አደጋ - የፈንጂዎቹ መገኛ መረጃ በኤሌክትሮኒክ መንገድ የሚመዘገብ ሲሆን፣ ፈንጂዎቹ ለቀጣይ ጽዳት እንዲያመቹ በተወሰነ ጊዜ ውስጥ በራሳቸው እንዲፈነዱ  ማድረግ ይቻላል።

ሁለትዮሽ ስልታዊ ጥቅም - ለጥቃት (የጠላትን የሎጂስቲክስ መስመር ለማቋረጥ) እና ለመከላከያ (ፈጣን የመከላከያ አጥር ለመፍጠር) ያገለግላል።

ኃይለኛ የጦር መሣሪያ- ፀረ-ታንክ ፈንጂዎቹ እንደ "ሊዮፓርድ" ወይም "ብራድሌይ" ያሉ ዘመናዊ ብረትለበስ ተሽከርካሪዎችን ሙሉ ለሙሉ የማውደም አቅም አላቸው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0