የሩሲያ 1 ቢሊዮን ዶላር ለሰላም ቦርድ የመመደብ ዝግጁነት ሞስኮ የታገዱባትን ንብረቶች የማስመለስ ተስፋዋን ቆርጣለች ማለት አይደለም - ክሬምሊን
19:35 22.01.2026 (የተሻሻለ: 19:44 22.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ 1 ቢሊዮን ዶላር ለሰላም ቦርድ የመመደብ ዝግጁነት ሞስኮ የታገዱባትን ንብረቶች የማስመለስ ተስፋዋን ቆርጣለች ማለት አይደለም - ክሬምሊን
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ በሰጡት መግለጫ ያነሷቸው ዋና ዋና ሃሳቦች፦
ሩሲያ ንብረቶቿን ለማስመለስ የምታደርገውን ትግል ትቀጥላለች፤ እንዲሁም ያሉትን አማራጮች ሁሉ ትጠቀማለች።
ሂደቱ ራሱ ከአሜሪካ ወገን የተወሰኑ እርምጃዎችን የሚጠይቅ ሲሆን፣ የሕግ ዝርዝሮቹም ገና መጣራት አለባቸው።
ሩሲያ ቀደም ሲል ከታገዱባት ንብረቶች ውስጥ 1 ቢሊዮን ዶላር ለሰላም ቦርድ ለመላክ ዝግጁ መሆኗን ቭላድሚር ፑቲን በትናንትናው ዕለት ማሳወቃቸው ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X