አውሮፓ 'ከሩሲያ ጋር ጦርነት ላይ አይደለችም፣' ገንዘቧንም መያዝ አትችልም - የቤልጂየም ጠቅላይ ሚኒስትር
15:50 22.01.2026 (የተሻሻለ: 15:54 22.01.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አውሮፓ 'ከሩሲያ ጋር ጦርነት ላይ አይደለችም፣' ገንዘቧንም መያዝ አትችልም - የቤልጂየም ጠቅላይ ሚኒስትር
“የአንድን አካል ገንዘብ ዝም ብሎ መውሰድ አይቻልም፤ (...) ይህ የጦርነት ተግባር ነው፣ ልናቃልለው አይገባም፤ በታሪክም ታይቶ የማይታወቅ ነው” ሲሉ ባርት ደ ዌቨር በዳቮስ እየተካሄደ ባለው የዓለም ኢኮኖሚ ፎረም ጎን ለጎን ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም፣ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት እንኳ ታግዶ የነበረ ገንዘብ ተወርሶ እንደማያውቅ የገለፁ ሲሆን፣ የታገደው የሩሲያ ሀብት ጉዳይ በዩክሬን ድርድር ወቅት የሚነሳ ይሆናል ብለዋል።
ባለፈው ዓመት፣ የአውሮፓ ኮሚሽን ለዩክሬን በሚሰጥ “ብድር” ስም የታገደውን የሩሲያ ሉዓላዊ ሀብት ለመውሰድ የአውሮፓ ኅብረት አባል ሀገራትን በከፍተኛ ሁኔታ ሲወተውት ነበር። ሆኖም በሕጋዊ እና በፋይናንስ ስጋቶች ምክንያት ስምምነት ላይ መድረስ አልተቻለም።
ሞስኮ፣ በበኩሏ ወደ 300 ቢሊዮን ዩሮ ገደማ የሚጠጋውን ሀብቷን መውረስ አስከፊ መዘዝ እንደሚያስከትል በተደጋጋሚ ስታስጠነቅቅ ቆይታለች። ፕሬዝዳንት ፑቲን ሃሳቡን “ዝርፊያ” ሲሉ የጠሩት ሲሆን፣ ይህ ድርጊት የዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት መሠረትን ሊያናጋ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X