የሞሮኮው ሮያል ኤር ማሮክ፣ በሴንት ፒተርስበርግ እና በአዲስ አበባ መካከል የቀጥታ በረራ ለመጀመር ማቀዱን አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየሞሮኮው ሮያል ኤር ማሮክ፣ በሴንት ፒተርስበርግ እና በአዲስ አበባ መካከል የቀጥታ በረራ ለመጀመር ማቀዱን አስታወቀ
የሞሮኮው ሮያል ኤር ማሮክ፣ በሴንት ፒተርስበርግ እና በአዲስ አበባ መካከል የቀጥታ በረራ ለመጀመር ማቀዱን አስታወቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 21.01.2026
ሰብስክራይብ

የሞሮኮው ሮያል ኤር ማሮክ፣ በሴንት ፒተርስበርግ እና በአዲስ አበባ መካከል የቀጥታ በረራ ለመጀመር ማቀዱን አስታወቀ 

ሮያል ኤር ማሮክ በሴንት ፒተርስበርግ እና በካዛብላንካ መካከል የቀጥታ በረራዎችን ጀምሯል።

​“ፑልኮቮ አውሮፕላን ማረፊያ (ሴንት ፒተርስበርግ የሚገኝ) በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሞሮኮ የመጣውን ቀጥተኛ በረራ አስተናግዷል” ሲል መግለጫው አመልክቷል።

​በረራዎቹ የሚከናወኑት በሮያል ኤር ማሮክ አየር መንገድ ሲሆን፣ በሳምንት ሦስት ቀናት ማለትም ሰኞ፣ ረቡዕ እና ቅዳሜ ይደረጋሉ። በረራዎቹ 160 መንገደኞችን የመጫን አቅም ባላቸው ቦይንግ 737-800 አውሮፕላኖች የሚከናወኑ ይሆናል።

የፑልኮቮ አውሮፕላን ማረፊያ የአቪዬሽን ኮሜርስ ዳይሬክተር አሲያ ካልቫሺ፣ “የፑልኮቮ የመጀመሪያው ቀጥተኛ በረራ ወደ ሞሮኮ መጀመሩ የአውሮፕላን ማረፊያውን ዓለም አቀፍ የበረራ መስመር ለማስፋፋት ትልቅ እርምጃ ነው። አፍሪካ ከፍተኛ የተሳፋሪዎች ቁጥር ዕድገት የሚታይባት ተስፋ ሰጪ ገበያ ነች። ወደፊት ወደ ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ አዲስ በረራዎችን የመጀመር፣ እንዲሁም ወደ ግብፅ እና ቱንዝያ የሚደረጉ በረራዎችን ድግግሞሽ የመጨመር ዕቅድ አለን” ሲሉ ተናግረዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0