ሩሲያ ከፕሬዝዳንታዊ ምርጫው በኋላ ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር ያላትን ግንኙነት 'ይበልጥ ለማጠናከር' ቁርጠኝነቷን አረጋገጠች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሩሲያ ከፕሬዝዳንታዊ ምርጫው በኋላ ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር ያላትን ግንኙነት 'ይበልጥ ለማጠናከር' ቁርጠኝነቷን አረጋገጠች
ሩሲያ ከፕሬዝዳንታዊ ምርጫው በኋላ ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር ያላትን ግንኙነት 'ይበልጥ ለማጠናከር' ቁርጠኝነቷን አረጋገጠች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 21.01.2026
ሰብስክራይብ

ሩሲያ ከፕሬዝዳንታዊ ምርጫው በኋላ ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር ያላትን ግንኙነት 'ይበልጥ ለማጠናከር' ቁርጠኝነቷን አረጋገጠች

​የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ ሞስኮ በታህሳስ ወር አጋማሽ ላይ በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ምርጫ "የሕዝብ ድምጽ አሰጣጥ ሂደት በሰላም መጠናቀቁን በደስታ ትቀበላለች"። በተጨማሪም "በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ የቅርብ ቅንጅት ለማድረግ" ያላትን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጣለች።

ሚኒስቴሩ በመግለጫው "የሩሲያ ወገን የመካከለኛው አፍሪካ ማኅበረሰብ በሂደት በተረጋጋ ፖለቲካዊ እና ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ልማት ጎዳና ላይ እንደሚራመድ ተስፋ ያደርጋል" ብሏል።

​ ታህሳስ 19 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ማካሄዷ ይታወሳል። በጥር ወር መጀመሪያ ይፋ በተደረገው ውጤት፣ በሥልጣን ላይ የሚገኙት ፕሬዝዳንት ፋውስቲን-አርካንጅ ቱዋዴራ 77.9 በመቶ ድምጽ በማግኘት በመጀመሪያው ዙር በድጋሚ ተመርጠዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0