ቱኒዚያ በከባድ ዝናብ ተመታች

ሰብስክራይብ

ቱኒዚያ በከባድ ዝናብ ተመታች

​በቱኒዚያ በተመዘገበ ከፍተኛ የዝናብ መጠን ምክንያት በትንሹ የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል። ዝናቡ መጠነ-ሰፊ የጎርፍ መጥለቅለቅ ያስከተለ ሲሆን፣ ባለሥልጣናት በተለያዩ ክልሎች ትምህርት እንዲቋረጥ ለማድረግ ተገደዋል።

​ ከሰኞ ምሽት ጀምሮ በዋና ከተማዋ ቱኒስ እንዲሁም በሀገሪቱ ሰሜናዊ እና ሰሜን ምስራቃዊ አካባቢዎች ከባድ ዝናብ እየጣለ ይገኛል።

​በከፍተኛ የዝናብ መጠን ምክንያት አንድ ግድብ ሞልቶ መፍሰሱ የጎርፍ መጥለቅለቁን ሁኔታ ይበልጥ አባብሶታል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0