ከ500 ሺህ በላይ የጤና ባለሙያዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የማኅበራዊ ጤና መድህን ሥርዓት ወደ ትግበራ ገብቷል - የኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት
21:15 20.01.2026 (የተሻሻለ: 21:24 20.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ከ500 ሺህ በላይ የጤና ባለሙያዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የማኅበራዊ ጤና መድህን ሥርዓት ወደ ትግበራ ገብቷል - የኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት
በዚህ ወር ሥራ የጀመረው ይህ ሥርዓት በአጠቃላይ ከኢትዮጵያ ሕዝብ 17 በመቶ የሚሆነውን የሚሸፍን ሲሆን፤ በመጀመሪያው ምዕራፍ የጤናው ዘርፍ ሠራተኞችን ተጠቃሚ ለማድረግ ከመስከረም ወር ጀምሮ የዝግጅት ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየቱን አገልግሎቱ ጨምሮ አስታውቋል።
የጤና መድህን ስርዓ ቱ በመደበኛው የኢኮኖሚ ክፍለ ጊዜ ተቀጥረው የሚሠሩ፦
የመንግሥት ሠራተኞችን፣
የጡረታ ባለመብቶችን እና
የልማት ድርጅት ሠራተኞችን ማዕከል ባደረገ መልኩ እንዲቀጥል እቅድ ተይዞለታል ሲሉ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X