- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

ግብርና እንደ የኃይል ምንጭ፦ የአፍሪካ የግብርና ልማት ጥያቄዎች

ግብርና እንደ የኃይል ምንጭ፦ የአፍሪካ የግብርና ልማት ጥያቄዎች
ሰብስክራይብ
"የኢትዮጵያ የግብርና ምርት 94 በመቶው በጥሬው ነው ወደ ውጭ የሚላከው። ምንም ዓይነት እሴት አይጨመርበትም። [...] እኔ ማየት የምፈልገው አፍሪካ ራሷን መመገብ ብቻ ሳይሆን ለቀሪው ዓለምም ምግብ ስታቀርብ ነው። አፍሪካ ምግብ ለመግዛት በየዓመቱ ከ120 ቢሊዮን ዶላር በላይ እያወጣች መቀጠል የለባትም ስለዚህ ራሷን መመገብ ብቻ ሳይሆን ከዚያም በላይ የምትተርፍ አፍሪካን፤ በቂ የምግብ ምርት ለውጭ ገበያ የምትልክ አፍሪካን ማየት እፈልጋለሁ።" ሲሉ የግብርና ሳይንቲስት እና ተመራማሪ ፀደቀ አባተ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በዚህ ባለ ሁለት ክፍል የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት በክፍል አንድ ከታዋቂው የግብርና ሳይንቲስት እና ተመራማሪ ፀደቀ አባተ (ዶ/ር) ጋር በመሆን አፍሪካ ለምን ልማቷን ለሌላ አካል አሳልፋ መስጠት እንደማትችል፤ እንደ እንሰት ካሉ የሀገር በቀል ሰብሎች አንስቶ እስከ መሬት ፖሊሲ እና ሌሎች ጉዳዮች እንወያያለን። በክፍል ሁለት ደግሞ ኢትዮጵያ እንደ ኦፓል ያሉ ውድ ማዕድናትን በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ለማካተት በምታደርገው እንቅስቃሴ ላይ በማተኮር፣ በማዕድን ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብስራት ከበደ (ዶ/ር) ጋር በመሆን ዳስሰነዋል።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0