የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያ ግብርና ማነቆዎችን ለመለየት 40 የትንተና ጥናቶችን ማከናወኑን አስታወቀ

የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያ ግብርና ማነቆዎችን ለመለየት 40 የትንተና ጥናቶችን ማከናወኑን አስታወቀ
ጥናቶቹ የሀገሪቱን የጎርጎሮሳውያኑ 2030 የግብርና ራዕይ ለማሳካት የሚያስችል መረጃን መሰረት ያደረገ ፍኖተ-ካርታ ለማዘጋጀት ያስችላሉ ሲል ኢንሰቲትዩት በዓመታዊ ሪፖርቱ አመልክቷል።
"ጥናቶቹ ስር የሰደዱ ማነቆዎችን በመለየትና የመፍትሄ ሃሳቦችን በተግባር በመሞከር፣ ለዘመናዊ፣ በገበያ ለሚመራ እና ሁሉን አቀፍ ለሆነ የግብርና ዘርፍ መሠረት እየጣሉ ነው" ሲሉ የኢንስቲትዩቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ማንደፍሮ ንጉሴ ለአገር ውስጥ ሚዲያ ገልፀዋል።
እንደ ኢንስቲትዩቱ መረጃ ጥናቶቹ፡-
ከ10 ሚሊዮን በላይ አርብቶ አደሮች የሚጠቀሙበት የግጦሽ መሬቶች ላይ የተደረገ የምርመራ ጥናት ብሔራዊ የግጦሽ መሬት ቁጥጥር ሥርዓት እንዲቋቋም መሠረት ጥሏል፡፡
ተቋሙ የሳተላይት እና የምድር መረጃን በማዋሃድ ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የወቅቱን የክትትልና የቅድመ ማስጠንቀቂያ የሚሰጥ ነው።
በ9 ክልሎች ውስጥ ለ6 ነጥብ 5 ሚሊዮን አርሶ አደሮች ተደራሽ የሆነ ሁለተኛው ምዕራፍ የግብርና ምርት የገበያ ትስስር ክላስተር ፕሮጀክት በጥናቱ ተካትቷል።
ጥናቶቹ ከግምት ይልቅ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ዘመናዊ አሰራርን በመፍጠር የኢትዮጵያ ዲጂታል ግብርና ፍኖተ ካርታን ደግፈዋል፡፡
ፖሊሲዎች ከጥናቶቹ ጋር በውጤታማነት እንዲጣጣሙ ከተደረጉ፣ ኢትዮጵያ ከሁለት እስከ ሦስት አስርት ዓመታት ውስጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ የስንዴ፣ በቆሎ፣ ቡና እና የወተት ተዋጽኦዎች ግንባር ቀደም አምራች ልትሆን ትችላለች።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X