አሜሪካ አፍሪካ ላይ በከፊል የጣለችው የቪዛ እገዳ ተፅዕኖው እምብዛም ነው - ኮትዲቯራዊ የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር
19:40 19.01.2026 (የተሻሻለ: 19:44 19.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አሜሪካ አፍሪካ ላይ በከፊል የጣለችው የቪዛ እገዳ ተፅዕኖው እምብዛም ነው - ኮትዲቯራዊ የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር
ዶናልድ ትራምፕ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ላይ የቪዛ ገደብ በመጣል፤ “አሜሪካ ለአሜሪካውያን” የሚለውን ፖሊሲ ተግባራዊ እያደረጉ ነው የሚሉት ኤሪክ ጎሬ ናቸው።
“ዶናልድ ትራምፕ በአፍሪካውያን አልተመረጡም፤ የተመረጡት በአሜሪካውያን ነው። ፖሊሲው በዋናነት የአሜሪካ ዜጎችን የሚጠቅም እና የኑሮ ሁኔታቸውን የሚያሻሽል ነው” ሲሉ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ይህ እርምጃ በተለይም በሚቀጥለው ሰኔ በሚጀምረው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ወቅት ከፍተኛ ፍልሰት ለመከላከል የታሰበ ነው ሲሉ ጎሬ አፅንዖት ሰጥተዋል።
የቪዛ ገደቡ በዋሽንግተን እና እገዳው በሚመለከታቸው የአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለውን የዲፕሎማሲ ግንኙነት ያን ያህል ይጉዳል ብለው እንደማያምኑም ገልጸዋል።
እንደ እሳቸው አባባል አሜሪካ "ሕጎቿን መጫኗን መቀጠሏ"፤ ለአፍሪካ ሀገራት ከመቀበል ውጭ ብዙ አማራጭ አይተውላቸውም።
“ከሁሉም በላይ ወሳኙ ነገር አፍሪካውያን ለጊዜው በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ እንደማይፈልጉ ማወቃቸው ነው” ሲሉ ደምድመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X