ዚምባብዌ ግብርናን ለማዘመን ለእያንዳንዱ መንደር ትራክተሮችን ልታቀርብ ነው
19:12 19.01.2026 (የተሻሻለ: 19:14 19.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዚምባብዌ ግብርናን ለማዘመን ለእያንዳንዱ መንደር ትራክተሮችን ልታቀርብ ነው
የዚምባብዌ መንግሥት በሁለተኛው ሀገራዊ የልማት ስትራቴጂ ሥር፤ ለ35 ሺህ መንደሮችን የትራክተር ለማቅረብ የሚያስችል የሜካናይዜሽን ፕሮግራም አስጀምሯል።
ይህ ተነሳሽነት ያነገባቸው ዓላማዎች፦
🟠 ግብርናን ማዘመን፣
🟠 የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣
🟠 የጉልበት ሥራን በሜካናይዜሽን በመተካት የገጠር ኢንዱስትሪ ልማትን ማፋጠን።
የዚህ ዕቅድ ዋነኛ አካል የመንደር ቢዝነስ ክፍሎችን ማቋቋም ነው። እነዚህ ማዕከላት በፀሐይ ኃይል የሚሠሩ የመስኖ አቅርቦቶችን፣ የአትክልት ስፍራዎችን፣ የዓሣ እርባታ እና የእንስሳት እርባታ መሠረተ ልማቶችን በማቅረብ ከእጅ ወደ አፍ ግብርናን ወደ ንግድ ሥራ ይቀይራሉ።
እነዚህን ክፍሎች ለመደገፍ ለመንደር አገልግሎት ተስማሚ የሆኑ አነስተኛ ትራክተሮች በማቅረብ ወቅቱን ለጠበቀ የእርሻ ልማት እና የመሬት ዝግጅት አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራሉ። የመንደር ቢዝነስ ክፍሎቹ የአካባቢያዊ የንግድ ማዕከል በመሆን ነዋሪዎች በጋራ እንዲያመርቱና ምርታቸውን ለገበያ እንዲያቀርቡ ዕድል ይሰጣሉ። ይህም በታችኛው የህብረተሰብ ክፍል የሥራ ዕድልን ከመፍጠሩም በላይ የቤተሰብ ገቢን ያሳድጋል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X