ፕሬዚዳንት ሙሴቪኒ ለሰባተኛ ጊዜ መመረጣቸውን ተከትሎ ኡጋንዳ የኢንተርኔት አገልግሎትን በከፊል መለሠች
16:59 19.01.2026 (የተሻሻለ: 20:04 19.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ፕሬዚዳንት ሙሴቪኒ ለሰባተኛ ጊዜ መመረጣቸውን ተከትሎ ኡጋንዳ የኢንተርኔት አገልግሎትን በከፊል መለሠች
አጠቃላይ የኢንተርኔት ትስስር ከምሽቱ 5 ሰዓት አካባቢ ቢመለስም፤ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች አሁንም እንደተዘጉ መሆናቸውን የአገልግሎት ሰጪ ኩባንያዎች ለደንበኞቻቸው አሳውቀዋል። እርምጃው መንግሥት የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾችን በከፊል ለማገድ ያወጣውን መመሪያ ተከትሎ የመጣ ነው።
ውሳኔው የንግድ ተቋማት ሥራቸውን እንዲቀጥሉ በማስቻል መንግሥት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የጣለው ገደብ እንደተጠበቀ እንዲቆይ የሚያደርግ መሆኑን የኤርቴል ኡጋንዳ ቃል አቀባይ ዴቪድ ቢሩንጊ አረጋግጠዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X