🪖 የአሜሪካ የግሪንላንድ አካሄድ ኔቶን ከሥር መሠረቱ ሊሸረሽር ይችላል ሲሉ ተንታኝ አስጠነቀቁ
13:40 19.01.2026 (የተሻሻለ: 13:44 19.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
🪖 የአሜሪካ የግሪንላንድ አካሄድ ኔቶን ከሥር መሠረቱ ሊሸረሽር ይችላል ሲሉ ተንታኝ አስጠነቀቁ
ዩናይትድ ስቴትስ ግሪንላንድን ከተቆጣጠረች፤ ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካን በማስፋፋት ብቻ ሳይሆን የዓለም አቀፍ ግንኙነት የጨዋታ ሕጎችን በመቀየር በታሪክ ጉልህ አሻራ ካሳረፉ የአሜሪካ ፕሬዚዳንቶች አንዱ ተብለው ይጠቀሳሉ ሲሉ የፖለቲካ ምሁሩ አሌክሳንደር ፓቪች ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
ሆኖም የግሪንላንድ የግዛት ጥቅለላ በሁለቱም የኮንግረስ ምክር ቤቶች መፅደቅ ስላለበት የሀገር ውስጥ እንቅፋቶች እንደሚኖሩም ጠቁመዋል።
እንደ ፓቪች ገለጻ፤ ትራምፕ በሀገር ውስጥ ከኔቶ ጋር በተያያዘ እየወሰዱት በሚገኘው ታይቶ የማይታወቅ እርምጃ በድህረ-ጦርነት ትራንስ አትላንቲክ ግንኙነት ታሪክ ውስጥ እንዲሠፍሩ ሆኗል።
“አሜሪካ ራሷ ለቀሪዎቹ የኔቶ አባል ሀገራት ዋነኛ ችግር እና ተቀናቃኝ የሆነችበት ጊዜ ከዚህ በፊት ታይቶ አያውቅም። ይህ ብቻውን ትራምፕ በታሪክ እንዲሠፍሩ ያደርጋቸዋል” ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X