ኢትዮጵያ ሥራ ፈጣሪ ወጣቶችን የሚደግፍ ኢንቨስትመንት ባንክ እያቋቋመች መሆኑ ተገለፀ
15:17 18.01.2026 (የተሻሻለ: 15:24 18.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ሥራ ፈጣሪ ወጣቶችን የሚደግፍ ኢንቨስትመንት ባንክ እያቋቋመች መሆኑ ተገለፀ
የሚቋቋመው ባንክ ሥራ ፈጣሪዎች ሐሳባቸውን ወደ መሬት ለማውረድ የሚያጋጥማቸውን የፋይናንስ ችግር በመሠረታዊነት ለመፍታት ያለመ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) አስታውቀዋል።
ባንኩ ተተኪ ምርቶችን ለማምረት፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለመጨመርና የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማስፋፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ማለታቸውን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
አክለውም የኢንቨስትመንት ባንኩ በሀገሪቱ ለሚታየው የሥራ ፈጠራ እንቅስቃሴ አዲስ ምዕራፍ እንደሚከፍት ገልፀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X