የዚምባብዌ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ከፍተኛ የፈተና ውጤት አስመዘገቡ
14:51 18.01.2026 (የተሻሻለ: 14:54 18.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የዚምባብዌ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ከፍተኛ የፈተና ውጤት አስመዘገቡ
የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ሚኒስትሩ ቶሬራይ ሞዮ፤ የ2025 የ "መደበኛ ደረጃ" የፈተና ውጤት ከ1980 ወዲህ ከፍተኛው ነው ሲሉ አወድሰውታል። ሚኒስትሩ፤ ተፈታኞች እና መምህራኖቻቸው 35.26 በመቶ የማለፍ ምጣኔ በማስመዝገባቸው እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። ውጤቱ ከ2024 33.19 በመቶ መሻሻል የታየበት ሲሆን ሚኒስቴሩ አሁን ግቡን ወደ 50 በመቶ ለማድረስ አዳዲስ ስልቶች በቅርቡ ይፋ እንደሚደረጉ አስታውቀዋል።
የፈተናውን ውጤት ዓርብ ዕለት ይፋ ያደረጉት የዚምባብዌ ትምህርት ቤቶች ፈተና ምክር ቤት የቦርድ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር ፖል ማፕፉሞ፤ ሴት ተማሪዎች ከወንዶች የተሻለ ውጤት እንዳስመዘገቡ ገልጸዋል፡፡
የማለፍ ምጣኔው፦
🟠 ለሴቶች 36.31 በመቶ፤
🟠 ለወንዶች 34.09 በመቶ ሆኗል።
ህዳር 2025 በተሰጠው ፈተና፤ በአጠቃላይ 302,066 እጩዎች ለፈተናው የተቀመጡ ሲሆን ከ2024 ጋር ሲነጻጸር የ3.7 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። ከእነዚህ ውስጥ 209,810 የሚሆኑት አምስት እና ከዚያ በላይ ትምህርቶችን ሲወስዱ፤ 73,978 የሚሆኑት ቢያንስ አምስቱን ትምህርቶች በ 'C' ግሬድ እና ከዚያ በላይ በሆነ ውጤት አልፈዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለጸገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X