የማሊ መንግሥት የሲቪል ድሮኖችን ለመቆጣጠር አዋጅ አወጣ

የማሊ መንግሥት የሲቪል ድሮኖችን ለመቆጣጠር አዋጅ አወጣ
ለሙያ፣ ለንግድ፣ ለመዝናኛ፣ ለግብርና እና ለፎቶግራፍ አገልግሎት የሚውሉ የሲቪል ድሮኖች ስርጭት በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ ይገኛል።
⏫ ለዚህ እድገት እንደ ምክንያት የተጠቀሱት፦
ዝቅተኛ ዋጋ፣
ለመጠቀም ቀላል መሆናቸው፣
የአገልግሎት አሰጣጥ ብቃታቸው እየተሻሻለ መምጣቱ።
ይሁን እንጂ ይህ መስፋፋት በርካታ ስጋቶችን አስከትሏል፦
የአየር ላይ ደህንነት፤ በተለይም በተከለከሉ ቀጣናዎች መብረር፣
የግል ሚስጥር እና የመረጃ ደህንነት ጥበቃ፣
አደገኛ በሆኑ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚጋረጡ አደጋዎች።
ከሁሉ በላይ አሳሳቢው እና ቀደም ሲል በሳህል ቀጣና የታየው ጉዳይ፤ ድሮኖች በታጣቂ ቡድኖች እጅ ገብተው ለሕገ-ወጥ ስለላ፣ ለቅኝት ወይም ፈንጂዎችንና አደገኛ ቁሶችን ለማጓጓዝ መዋላቸው ነው።
እነዚህን አደጋዎች ለመፍታት በጸጥታና ሲቪል ጥበቃ ሚኒስትሩ የቀረበው አዲስ ረቂቅ አዋጅ ዓላማዎች፦
የድሮኖችን ግዢ፣ ይዞታ እና አጠቃቀም በጥብቅ መቆጣጠር፣
የአብራሪዎችን እና የኦፕሬተሮችን ግዴታዎች በግልጽ ማስቀመጥ፣
ድሮኖችን ተገቢ ላልሆነ አገልግሎት ወይም ለሽብር ተግባራት እንዳይውሉ የመከላከል ሥራን ማጠናከር፣
የአየር ክልልን እና የሕዝብን ደህንነት መጠበቅ።
አዋጁ ድሮኖችን ሙሉ በሙሉ አይከለክልም፡፡ ይልቁንም እንደ ዘመናዊ ግብርና፣ ካርታ ሥራ እና የቪዲዮ ምርት ያሉ የፈጠራ ሥራዎች እንዲከናወኑ የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ይፈጥራል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X