የሕንድ መንግሥት ለሴት ከፍተኛ አመራሮች የአጭር ጊዜ የሥልጠና ፕሮግራም አዘጋጀ
18:00 17.01.2026 (የተሻሻለ: 18:14 17.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሕንድ መንግሥት ለሴት ከፍተኛ አመራሮች የአጭር ጊዜ የሥልጠና ፕሮግራም አዘጋጀ
የሥልጠና ዕድሉ የሕንድና የኢትዮጵያ ከፍተኛ ስትራቴጂያዊ የሁለትዮሽ ግንኙኝነት ማሳያ እንደሆነ፤ የሴቶችና ማኅበራዊ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ በኢትዮጵያ የሕንድ አምባሳደር ሸሪ አኒል ኩማር ራዪ ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ተነስቷል።
ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬን ጨምሮ ከፓርላማ፣ ከኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን፣ ከተለያዩ የሴት አደረጃጀቶች እና ከክልሎች የተውጣጡ ከፍተኛ ሴት አመራሮች ከዚህ በፊት የሕንድ ሥልጠና ዕድል ተጠቃሚ እንደነበሩም ተመላክቷል።
በቀጣይ የሕንድ መንግሥት ለአመራሮች የሚሰጣቸውን የተለያዩ የአጭር ጊዜ ሥልጠና እና የረዥም ጊዜ የትምህርት ዕድሎችን ለማመቻቸት የሕንድ ኤምባሲ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ የሴቶችና ማኅበራዊ ሚኒስቴር ገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X