የጊኒ ፕሬዚዳንት በዓለ ሲመት ተጀመረ
17:36 17.01.2026 (የተሻሻለ: 17:44 17.01.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የጊኒ ፕሬዚዳንት በዓለ ሲመት ተጀመረ
ማማዲ ዱምቡያ የቃለ መሃላ ሥነ-ሥርዓት በመፈጸም የመጀመሪያ የፕሬዚዳንትነት ዘመናቸውን በይፋ ለመጀመር በኖንጎ ጄኔራል ላንሳና ኮንቴ ስታዲየም ደርሰዋል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የማሊ፣ የሩዋንዳ፣ የሴራሊዮን፣ የሴኔጋል፣ የጋቦን፣ የሞሪታኒያ እና የላይቤሪያ ፕሬዝዳንቶች፤ የቻይና፣ የጋና እና የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንቶች፤ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር እና ሌሎች ከፍተኛ ባለሥልጣናት ተገኝተዋል።
የጊኒ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ታኅሣሥ 19 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደ ሲሆን ዱምቡያ ከተሰጡ ድምፆች 86.72 በመቶ በማግኘት አሸንፈዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

