የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት የማዳጋስካር የሽግግር መሪን ተቀብለው አነጋገሩ
16:08 17.01.2026 (የተሻሻለ: 16:44 17.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት የማዳጋስካር የሽግግር መሪን ተቀብለው አነጋገሩ
በፕሪቶሪያ ከፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ ጋር የተገናኙት ኮሎኔል ማይክል ራንድሪያኒሪና፤ ስለ ማዳጋስካር ፖለቲካዊ ሽግግር፣ ለመካሄድ ስለታቀደው ብሔራዊ ምክክር እንዲሁም ሰላማዊ ሂደት ለመፍጠር እየተወሰዱ ስላሉ እርምጃዎች ማብራሪያ እንደሰጡ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
ፕሬዚዳንት ራማፎሳ በበኩላቸው፤ "በተቻለ ፍጥነት ወደ ምርጫ የሚመራ" ሁሉንም ወገኖች ያካተተ ውይይት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።
የደቡብ አፍሪካ ልማት ማኅበረሰብ የማዳጋስካርን ሽግግር ለመደገፍ "የአዋቂዎች ቡድን" ለመላክ ያስተላለፈውን ውሳኔ ፕሬዚዳንቱ በድጋሚ ማረጋገጣቸውን መግለጫው አክሎ አመልክቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia
/ 
© telegram sputnik_ethiopia
/