የአማራ ክልል መዲና ዘመናዊ የኤሌክትሪክ አውቶብሶች አገልግሎት አስጀመረች
15:45 17.01.2026 (የተሻሻለ: 07:14 18.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የአማራ ክልል መዲና ዘመናዊ የኤሌክትሪክ አውቶብሶች አገልግሎት አስጀመረች
የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር በበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የተገጣጠሙና በኤሌክትሪክ የሚሠሩ 10 ዘመናዊ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ አውቶብሶችን ሥራ አስጀምሯል።
የከተማ አውቶብሶቹ በከተማው በአሁኑ ሠዓት የሚታየውን ከፍተኛ የትራንስፖርት እጥረት እንደሚያቃሉ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ ዘግቧል።
እርምጃው መንግሥት የነዳጅ ወጪና የውጭ ምንዛሪን ለማስቀረት እንዲሁም የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ የያዘው እቅድ አካል ነው ተብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X