የአማራ ክልል መዲና ዘመናዊ የኤሌክትሪክ አውቶብሶች አገልግሎት አስጀመረች
15:45 17.01.2026 (የተሻሻለ: 07:14 18.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአማራ ክልል መዲና ዘመናዊ የኤሌክትሪክ አውቶብሶች አገልግሎት አስጀመረች
የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር በበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የተገጣጠሙና በኤሌክትሪክ የሚሠሩ 10 ዘመናዊ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ አውቶብሶችን ሥራ አስጀምሯል።
የከተማ አውቶብሶቹ በከተማው በአሁኑ ሠዓት የሚታየውን ከፍተኛ የትራንስፖርት እጥረት እንደሚያቃሉ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ ዘግቧል።
እርምጃው መንግሥት የነዳጅ ወጪና የውጭ ምንዛሪን ለማስቀረት እንዲሁም የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ የያዘው እቅድ አካል ነው ተብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X