የጋና ወታደራዊ ፖሊስ በታሪክ የመጀመሪያዋን ሴት አዛዥ ሾመ
15:17 17.01.2026 (የተሻሻለ: 16:24 17.01.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የጋና ወታደራዊ ፖሊስ በታሪክ የመጀመሪያዋን ሴት አዛዥ ሾመ
ሌተናል ኮሎኔል ጃክሊን ዴላ ጋሌ የጋና ወታደራዊ ፖሊስን በመምራት የመጀመሪያዋ ሴት እንደሚሆኑ የጋና ጦር ሠራዊት ገልጿል።
ሹመቱ የሀገሪቱ ጦር የሥርዓተ-ጾታ እኩልነትን ለማስፈንና በብቃት ላይ የተመሠረተ አመራርን ለመገንባት ለጀመረው ቁርጠኝነት እንደ ትልቅ እርምጃ ታይቷል ሲል የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
የጋና ወታደራዊ ፖሊስ በጦር ኃይሉ ውስጥ ዲሲፕሊን በማስከበር፣ ወታደራዊ ወንጀሎችን በመመርመር እና የወታደራዊ ተቋማትን ደህንነት በመጠበቅ ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታል ተብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

