የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ የአኅጉሪቱ እግር ኳስ “ከፍተኛ እድገት ያሳየበት ነው” - ባለሙያ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየ2025 የአፍሪካ ዋንጫ የአኅጉሪቱ እግር ኳስ “ከፍተኛ እድገት ያሳየበት ነው” - ባለሙያ
የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ የአኅጉሪቱ እግር ኳስ “ከፍተኛ እድገት ያሳየበት ነው” - ባለሙያ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 17.01.2026
ሰብስክራይብ

የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ የአኅጉሪቱ እግር ኳስ “ከፍተኛ እድገት ያሳየበት ነው” - ባለሙያ

በአጠቃላይ በውድድሩ የታየው የጨዋታ ጥራት “በጣም የሚያስደንቅ” እንደነበር የስፖርት ንግድ ባለሙያ እና የፓልማሬስ ወርልድ ዳይሬክተር ናስር ንጆያ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

“ግማሽ ፍጻሜዎቹ በምዕራቡ ዓለም በሚደረጉ አንዳንድ ጨዋታዎች ላይ እንኳን የሚታዩ ስህተቶች ያልነበሩባቸው ነበሩ። ጨዋታው በከፍተኛ ሁኔታ ተሻሽሏል። አብዛኛዎቹ ተጫዋቾችም በአውሮፓ ካሉ ምርጥ 10 ሊጎች የተውጣጡ ናቸው።”

ባለሙያው የሀገር ውስጥ አሠልጣኞች ስኬትንም አድንቀዋል።

“[በእሁዱ] ፍጻሜ ሴኔጋላዊ እና ሞሮኳዊ አሠልጣኞች ይገናኛሉ። ስለዚህ አዲሱ የአፍሪካ ዋንጫ በአፍሪካዊ አሠልጣኝ በሚመራ ሀገር ይወሰዳል ማለት ነው። ይህ በተከታታይ ለአራተኛ ጊዜ የሚመዘገብ ስኬት ነው። ይህም ለአፍሪካ ወጣቶች ‘ችሎታችሁን አሳዩ፤ በአኅጉሪቱ የሚገባችሁን ቦታም ያዙ’ የሚል ጠንካራ መልዕክት ያስተላልፋል።”

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0