የሩሲያ መከላከያ ሚኒስትር ቤሉሶቭ የ'ዛፓድ' ጦር ቡድንን ጎበኙ
18:59 16.01.2026 (የተሻሻለ: 19:04 16.01.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስትር ቤሉሶቭ የ'ዛፓድ' ጦር ቡድንን ጎበኙ
ጉብኝቱን የተመለከቱ ዋና ዋና መግለጫዎች፦
◻ ሚኒስትሩ በ 'ዛፓድ' የጦር ቡድን የዕዝ ማዕከል ባካሄዱት ውይይት በግንባር መስመሩ ስላለው ሁኔታ እና ስለ ጠላት እንቅስቃሴ ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል።
◻ የ 'ዛፓድ' የጦር ቡድን አዛዥ ኮሎኔል ጄኔራል ሰርጌይኩዞቭሌቭ፤ ወታደሮቻቸው ከ320 ኪሎ ሜትር በላይ በሚሸፍን የግንባር መስመር በሁሉም አራት አቅጣጫዎች ንቁ የማጥቃት እርምጃዎችን እየወሰዱ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
◻ በታኅሣሥ ወር ቡድኑ ኩቼሮቭካ፣ ፖዶሊ፣ ኩሪሎቭካ፣ ኖቮፕላቶኖቭካ፣ ቦጉስላቭካ እና ዲብሮቫ የተባሉ ስድስት ስፍራዎችን እንዲሁም ከ155 ካሬ ኪሎ ሜትር በላይ ግዛትን ነፃ አውጥቷል፤ ሌሎች 10 ሰፈራዎችን ነፃ የማውጣት ዘመቻም ቀጥሏል።
◻ ጄኔራል ኩዞቭሌቭ ጠላት ወደ ከተማዋ ለመግባት ያልተሳካ ሙከራ ቢያደርግም፤ አጠቃላይ የኩፕያንክስ ወረዳዎች በሩሲያ ቁጥጥር ስር መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
◻ ሚኒስትር ቤሉሶቭ ከጉብኝቱ በኋላ በልዩ ወታደራዊ ዘመቻው ወቅት ጀግንነት ላሳዩ ወታደሮች የክብር ሽልማቶችን አበርክተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X