የቻድ ፕሬዚዳንት ማሃማት ኢድሪስ ዴቢ ኢትኖ የ2026 የአፍሪካ የሰላም ሽልማት ተሸላሚ ሆኑ

© telegram sputnik_ethiopiaየቻድ ፕሬዚዳንት ማሃማት ኢድሪስ ዴቢ ኢትኖ የ2026 የአፍሪካ የሰላም ሽልማት ተሸላሚ ሆኑ
የቻድ ፕሬዚዳንት ማሃማት ኢድሪስ ዴቢ ኢትኖ የ2026 የአፍሪካ የሰላም ሽልማት ተሸላሚ ሆኑ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 16.01.2026
ሰብስክራይብ

የቻድ ፕሬዚዳንት ማሃማት ኢድሪስ ዴቢ ኢትኖ የ2026 የአፍሪካ የሰላም ሽልማት ተሸላሚ ሆኑ

ፕሬዚዳንቱ ለዚህ ሽልማት የበቁት የሀገሪቱን የፖለቲካ ሽግግር በሰላማዊ መንገድ በመምራታቸው እና ለሱዳን ስደተኞች ሰብዓዊ መጠለያ በመስጠታቸው ነው።

በጄኔቫ ስብሰባውን ያካሄደው የአፍሪካ የሰላም ጉባኤ ኮሚቴ በሙሉ ድምፅ ውሳኔ ሽልማቱ እንዲሰጥ ወስኗል።

የሽልማቱ ዳኞች ፕሬዚዳንቱ የፖለቲካ ሽግግሩን ወደ ግጭት ሳያመራ በመምራት ላሳዩት ብቃት፣ ለውይይት እና ለተቋማት መረጋጋት ቁርጠኛ መሆናቸውን እንዲሁም ቻድ ለሱዳን ቀውስ በአብሮነት ምላሽ መስጠቷን አድንቀዋል።

ይፋዊ የሽልማት ሥነ-ሥርዓቱ በየካቲት ወር መጀመሪያ በሞሪታኒያ መዲና ኑዋክቾት እንዲካሄድ ታቅዷል።

የአፍሪካ የሰላም ሽልማት ለአህጉራዊ መረጋጋት ቁርጠኛ ለሆኑ የአፍሪካ መሪዎች በየዓመቱ የሚሰጥ እውቅና ነው። ከዚህ ቀደም የኒጀሩ ሞሃመድ ባዙም፣ የናይጄሪያው ሙሃማዱ ቡሃሪ፣ የጋምቢያው አዳማ ባሮው እና የኮትዲቯሩ አላሳን ኦዋታራ የዚህ ሽልማት ተሸላሚ ነበሩ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0