ኢትዮጵያና ሕንድ በቅመማ ቅመም እና በመድኃኒት ዕፅዋት ዘርፍ በአጋርነት ለመሥራት ተስማሙ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያና ሕንድ በቅመማ ቅመም እና በመድኃኒት ዕፅዋት ዘርፍ በአጋርነት ለመሥራት ተስማሙ
ኢትዮጵያና ሕንድ በቅመማ ቅመም እና በመድኃኒት ዕፅዋት ዘርፍ በአጋርነት ለመሥራት ተስማሙ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 16.01.2026
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያና ሕንድ በቅመማ ቅመም እና በመድኃኒት ዕፅዋት ዘርፍ በአጋርነት ለመሥራት ተስማሙ

በኢትዮጵያ የሕንድ ኤምባሲ ከሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቱ ጋር በመተባባር ባዘጋጀው ልዩ መድረክ ላይ ሁለቱ ሀገራት የጀመሩት አጋርነት የኢትዮጵያን የወጪ ንግድ አቅም ለማሳደግ እና የሕንድን የቴክኖሎጂ ተሞክሮ ለመጠቀም ያለመ ነው ተብሏል።

ዝንጅብል፣ እርድ፣ ቅመሞች እና ማሽላ በልዩ ሁኔታ ትኩረት እንደተደረገባቸው ኤምባሲው ባወጣው መግለጫ አመላክቷል፡፡

ኢትዮጵያ ከፍተኛ እሴት የተጨመረባቸው እና ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶች ወደ ውጪ እንድትልክ ሕንድ “በጥራት አቢዮት” ያካበተችውን ልምድ በማካፈል ድጋፍ ማድረግ በምትችልበት መንገድ ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል፡፡

በተጨማሪም ሀገሪቱ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣናን በመጠቀም የምስራቅ አፍሪካ የምግብ ማቀነባበሪያ ማዕከል ለመሆን በቀረፀችው ስትራቴጂ ዙሪያ ምክክር ተደርጓል፡፡

ይህ አጋርነት በቅርቡ የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ባደረጉት ታሪካዊ ጉብኝት እና የሁለትዮሽ ውይይት ወቅት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ “ስትራቴጂካዊ አጋርነት” ለማሳደግ ከስምምነት መድረሳቸውን ተከትሎ የመጣ ነው፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0