ለኖርድ ስትሪም ፍንዳታ ተጠያቂ የሆኑትን አካላት ይፋ እና ተጠያቂ የማድረጊያ ጊዜው አሁን ነው - ክሬምሊን
17:22 16.01.2026 (የተሻሻለ: 17:24 16.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ለኖርድ ስትሪም ፍንዳታ ተጠያቂ የሆኑትን አካላት ይፋ እና ተጠያቂ የማድረጊያ ጊዜው አሁን ነው - ክሬምሊን
“ማን እንደፈጸመው አስቀድሞ በደንብ ይታወቃል” ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ፤ የጀርመን ጠቅላይ ፍርድ ቤት በኖርድ ስትሪም የጋዝ ቧንቧ ፍንዳታ ላይ በሰጠው የቅርብ ጊዜ ውሳኔ ዙሪያ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል።
የጀርመን ጠቅላይ ፍርድ ቤት እ.ኤ.አ 2022 የተፈጸመውን የኖርድ ስትሪም የጋዝ ቧንቧ መስመር ፍንዳታ በማቀናጀት የተጠረጠረው የዩክሬን ዜጋ ሰርሂ ኩዝኔትሶቭ በቁጥጥር ስር ውሎ እንዲቆይ ባለፈው ሐሙስ ወስኗል።
በጣሊያን ከተያዘ በኋላ ለጀርመን ተላልፎ የተሰጠው ኩዝኔትሶቭ፤ የጥፋት ድርጊቱን “በውጭ ሀገር መንግሥት” ትዕዛዝ ሳይፈፅም አይቀርም የሚል ከፍተኛ ግምት እንዳለ ፍርድ ቤቱ ገልጿል።
ያለ ምንም ማወላዳት ለኖርድ ስትሪም ፍንዳታ ተጠያቂው ማን እንደሆነ ለመግለጽ እና ኃላፊነቱን ማን እንደሚወስድ ለመወሰን ጊዜው አሁን ደርሷል ሲሉ ፔስኮቭ ንግግራቸውን አጠቃለዋል።
በኖርድ ስትሪም የጋዝ ቧንቧዎች ላይ ምን እንደተከሰተ ስፑትኒክ አፍሪካ ያዘጋጀውን ዝርዝር ትንታኔ ያንብቡ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X