ትራምፕ የጋዛ የሰላም ዕቅድ ሁለተኛ ምዕራፍ መጀመሩን ይፋ አደረጉ
10:42 16.01.2026 (የተሻሻለ: 10:44 16.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ትራምፕ የጋዛ የሰላም ዕቅድ ሁለተኛ ምዕራፍ መጀመሩን ይፋ አደረጉ
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ያወጡትን መግለጫ ተከትሎ፤ ዩናይትድ ስቴትስ የጋዛን ግጭት ለመፍታት ያዘጋጀችው ባለ 20 ነጥብ ዕቅድ "በይፋ ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ተሸጋግሯል" ብለዋል።
ሁለተኛው ምዕራፍ ከተኩስ አቁም ወደ ትጥቅ መፍታት፣ በባለሙያዎች ወደሚመራ አስተዳደር እና ወደ መልሶ ግንባታ እንደሚሸጋገር እንዲሁም እሳቸው በሚመሩት ዓለም አቀፍ "የሰላም ቦርድ" ስር የሽግግር ወቅት "የጋዛ አስተዳደር ብሔራዊ ኮሚቴ" የተሰኘ የፍልስጤም የባለሙያዎች አስተዳደር ምስረታን እንደሚያካትት ተናግረዋል።
"የሰላም ቦርዱ ሰብሳቢ እንደመሆኔ፤ በቦርዱ ከፍተኛ ተወካይ በመታገዝ በሽግግር ወቅት ጋዛን የሚያስተዳድረውን አዲሱን የፍልስጤም የባለሙያዎች መንግሥት፤ የጋዛ አስተዳደር ብሔራዊ ኮሚቴን፤ እደግፋለሁ" ብለዋል።
በሁለተኛው ምዕራፍ በግብፅ፣ ቱርክ እና ኳታር ድጋፍ የጦር መሳሪያዎችን ማስረከብ እና ዋሻዎችን ማፍረስ ጨምሮ ሃማስ ሙሉ በሙሉ ትጥቅ እንዲፈታ እንደሚደርግ ትራምፕ አመልክተዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X