አሜሪካ በኢራን ዙሪያ ውጥረት እና አለመረጋጋትን እያቀጣጠለች ነው - በተባበሩት መንግሥታት የሩሲያ መልዕክተኛ
10:16 16.01.2026 (የተሻሻለ: 10:24 16.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አሜሪካ በኢራን ዙሪያ ውጥረት እና አለመረጋጋትን እያቀጣጠለች ነው - በተባበሩት መንግሥታት የሩሲያ መልዕክተኛ
በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሩሲያ ቋሚ መልዕክተኛ ቫሲሊ ኔቤንዚያ፤ አሜሪካ በኢራን ዙሪያ ውጥረት የማባባስ እና ግርግር የመፍጠር ሥራዋን ቀጥላለች ብለዋል።
ኔቤንዚያ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ሩሲያ ለኢራን ሕዝብ ያላትን አጋርነት ትገልጻለች።
ባዕድ የጠላት ኃይሎች አሁን ያለውን ሁኔታ በመጠቀም የማይፈልጉትን የፖለቲካ ሥርዓት ለመገልበጥ እየሞከሩ ነው።
ዋሽንግተን በኢራን ላይ የምትጠቀመው ንግግር እጅግ አደገኛ እና ኃላፊነት የጎደለው ነው።
በኢራን እየተከሰተ ያለው ሁኔታ ሌላኛው የ “ቀለም አብዮት” ስልትን ይመስላል።
አሜሪካ እና ደጋፊዎቿ በምዕራባውያን የተፈጠሩትን የኢራን የውስጥ ችግሮች ሀገሪቱን ለማወክ እየተጠቀሙባቸው ነው።
ሩሲያ አሜሪካ እንደ የዓለም ዳኛ መመሰሏን እና ውጥረት የሚያባብሱ ድርጊቶቿን እንድታቆም ታሳስባለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X