አሜሪካ ኢራንን አዲሷ ሊቢያን ማድረግ ትፈልጋለች ሲሉ የፖለቲካ ተንታኝ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱአሜሪካ ኢራንን አዲሷ ሊቢያን ማድረግ ትፈልጋለች ሲሉ የፖለቲካ ተንታኝ ተናገሩ
አሜሪካ ኢራንን አዲሷ ሊቢያን ማድረግ ትፈልጋለች ሲሉ የፖለቲካ ተንታኝ ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 15.01.2026
ሰብስክራይብ

አሜሪካ ኢራንን አዲሷ ሊቢያን ማድረግ ትፈልጋለች ሲሉ የፖለቲካ ተንታኝ ተናገሩ

​ኢራን ውስጥ ግጭት መከሰቱ አይቀሬ መሆኑን የቴህራን ዩኒቨርሲቲው የፖለቲካ ተንታኝ ፉአድ ኢዛዲ ለስፑትኒክ ገልፀዋል። ዋሽንግተን ባለፈው ሰኔ ሀገሪቱን ኢላማ ማድረጓን በማስታወስ የሚከተለውን ብለዋል፦

​“አሜሪካ እና እስራኤል አሁንም የጦርነት አስተሳሰብ አላቸው፤ ቀደም ሲል በኢራን ላይ ጥቃት ሰንዝረው የነበረ ቢሆንም ዓላማቸውን ግን አላሳኩም። አሁን ደግሞ ሌሎች እቅዶች አሏቸው።”

​የኢራን ህዝብ ከሊቢያ ትምህርት መውሰዱንና ዋሽንግተን “ለሰብአዊ መብቶች ምንም ዓይነት ክብር እንደሌላት” እንደሚገነዘቡም ጠቁመዋል።

​ እንደ ተንታኙ ገለጻ፣ አሜሪካ ከባህር ሰርጓጅ መርከቦች የሚተኮሱ የሚሳኤል ጥቃቶችን አማራጭ ልታደርግ ትችላለች።

​“ይሁን እንጂ ይህ ትልቅ ስህተት ይሆናል። የኢራን ባለስልጣናት በዚህ ጊዜ በከፍተኛ ኃይል ምላሽ ለመስጠት ወስነዋል፤ እንዲህ ዓይነቱ የአሜሪካ ጥቃት ቀጣናው ውስጥ መጠነ ሰፊ እና ከባድ ጦርነት እንዲቀሰቀስ ብቻ ነው የሚያደርገው።”

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0