ሩሲያ ለማዳጋስካር ወታደራዊ ቁሳቁሶችን አስረከበች፤ ሥልጠናም እንደምትሰጥ የማዳጋስካር ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ
19:54 15.01.2026 (የተሻሻለ: 20:04 15.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ ለማዳጋስካር ወታደራዊ ቁሳቁሶችን አስረከበች፤ ሥልጠናም እንደምትሰጥ የማዳጋስካር ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ
የሩሲያ ልዑካን ቡድን፣ ለማዳጋስካር ጦር ሰራዊት የወታደራዊ ቁሳቁስ ጭነት ያስረከበ ሲሆን፣ በቅርብ ቀናት ውስጥም የሩሲያ ባለሙያዎች የመሣሪያዎቹን አጠቃቀም የተመለከተ ሥልጠና እንደሚሰጡ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
ሥልጠናው በዋና ከተማዋ አንታናናሪቮ አቅራቢያ የሚገኙ የጦር ክፍሎችን የሚያካትት ይሆናል።
እንደ ጽሕፈት ቤቱ ገለጻ፣ በሶቪዬት ዘመን የቀረቡ የካላሽንኮቭ ጠመንጃዎችን ጨምሮ በሩሲያ የተሰሩ የጦር መሣሪያዎች በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ውስጥ በብዛት ጥቅም ላይ የሚውሉ የጦር መሣሪያ ዓይነቶች ናቸው።
ይህ አቅርቦት የተከናወነው፣ የሀገሪቱ ጊዜያዊው ፕሬዝዳንት ሚካኤል ራንድሪያኒሪና በታህሳስ ወር መጀመሪያ ላይ ሀገሪቱ ከሩሲያ ጋር ለሚደረጉ ትብብሮች ዝግጁ መሆኗን ማረጋገጣቸውን ተከትሎ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

