ኢትዮጵያ በጅቡቲ በኩል የነዳጅ እና የማዳበሪያ ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ ቀጠናዊ ንግድን ልታሳድግ መሆኑን የጅቡቲው ባለሥልጣን ገለፁ
15:43 15.01.2026 (የተሻሻለ: 15:54 15.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ በጅቡቲ በኩል የነዳጅ እና የማዳበሪያ ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ ቀጠናዊ ንግድን ልታሳድግ መሆኑን የጅቡቲው ባለሥልጣን ገለፁ
ይህ እንቅስቃሴ ሀገሪቱ የውጭ ምርቶችን ከማስገባት ይልቅ ወደ ውጭ በመላክ ላይ ወደተመሰረተ የምጣኔ ሀብት ሞዴል ለማሸጋገር ያላትን ስትራቴጂያዊ እቅድ የሚያንፀባርቅ ነው ሲሉ የጅቡቲ ወደቦችና ነፃ የንግድ ቀጣና ባለሥልጣን ኃላፊ አብዲቃድር ኡመር ሀዲ ለጂቡቲ ሚዲያ በሰጡት ቃለ መጠይቅ አሳውቀዋል፡፡
"ኢትዮጵያ ከውጭ የምታስገባውን በመቀነስ የምትልከውን ለመጨመር ትሻለች፡፡ አንድ ሀገር ከፍጆታዋ በላይ ስታመርት ኢኮኖሚዋ እየጠነከረ ይሄዳል" በማለት ጅቡቲ ለውጡን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን አብዲቃድር ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት 1.8 ሚሊየን ቶን የግብርና ማዳበሪያ ታስገባለች ያሉት ባለሥልጣኑ፣ አሁን ግን የነዳጅ ምርቶችን እና የግብርና ግብዓቶችን ወደ ውጭ ለመላክ አቅዳለች፤ ጅቡቲም ቀዳሚ የሎጂስቲክስ መተላለፊያ ሆና ታገለግላታለች ብለዋል።
ከሰሞኑ ወደ ጅቡቲ የሥራ ጉብኝት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዶራሌህ ሁለገብ ወደብ እና የሆራይዘን ነዳጅ ተርሚናልን ጎብኝተዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X