የሩሲያ ፌዴራል የደህንነት አገልግሎት የእንግሊዝን የመረጃ መኮንን መለየቱን አስታወቀ
11:35 15.01.2026 (የተሻሻለ: 11:44 15.01.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ ፌዴራል የደህንነት አገልግሎት የእንግሊዝን የመረጃ መኮንን መለየቱን አስታወቀ
የሩሲያ የፌዴራል የደህንነት አገልግሎት (ኤፍኤስቢ) እንዳስታወቀው፣ ዴቪስ ጋሬዝ ሳሙኤል ተብሎ የሚጠራ የመረጃ (የስለላ) መኮንን፣ በሞስኮ በሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ የአስተዳደርና ኢኮኖሚ ክፍል ሁለተኛ ፀሐፊ በመሆን ሽፋን ወደ ሩሲያ ተልኮ ነበር።
ይህ የእንግሊዝ ዜጋ የዲፕሎማቲክ እውቅናው የተሰረዘ ሲሆን፣ በሁለት ሳምንታት ውስጥም ከአገር እንዲወጣ መታዘዙን መሥሪያ ቤቱ ገልጿል።
ቀደም ብሎ በዛሬው ዕለት፣ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጊዜያዊነት የተሾሙትን የእንግሊዝ ጉዳይ አስፈፃሚ ዴኒ ዶላኪያን (በቪዲዮው ላይ የሚታዩት) አስጠርቶ አነጋግሯል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X