አዳዲስ ግጭቶች መከሰታቸው ቢዘገብም፣ የደቡብ ሱዳን የሰላም ሂደት በትክክለኛው መስመር ላይ የሚገኝና የማይቀለበስ መሆኑን ሚኒስትሩ ገለጹ

አዳዲስ ግጭቶች መከሰታቸው ቢዘገብም፣ የደቡብ ሱዳን የሰላም ሂደት በትክክለኛው መስመር ላይ የሚገኝና የማይቀለበስ መሆኑን ሚኒስትሩ ገለጹ
የስምንት ዓመታት እድሜ ያለው የሰላም ስምምነት ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን እና በሀገሪቱ ያሉ የመንግሥት አካላት በሙሉ ከፍተኛ መረጋጋት እያሳዩ መሆናቸውን የደቡብ ሱዳን የጆንግሌይ ግዛት የፋይናንስ፣ ፕላን እና ኢንቨስትመንት ሚኒስትር ዶንጌ ጋይ ዶንጌ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
በጆንግሌይ ስላለው ሁኔታ የሚኒስትሩ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
🟠 በሰራዊቱ እና በተቃዋሚ ኃይሎች መካከል በቅርቡ የተከሰቱ ውጥረቶች በሁለት ትናንሽ አካባቢዎች ብቻ የተገደቡ እንጂ አጠቃላይ የሰላም ሂደቱን አደጋ ላይ የሚጥሉ አይደሉም፡፡
🟠 ግጭቶቹ ተነጥለው የሚታዩ ክስተቶች ናቸው፤ የመንግሥት ኃይሎች በሰላማዊ ሰዎች እና በወታደሮች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ለማድረግ ሲሉ ስልታዊ በሆነ መንገድ ከቦታዎቹ ለቀው ወጥተዋል፡፡
🟠 ምንም እንኳን ስርዓት አልበኛ በሆኑ የተቃዋሚ ኃይሎች ትንኮሳዎች ቢኖሩም፣ መንግሥት የሰላም ስምምነቱን ተግባራዊ ለማድረግ ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ነው፡፡
🟠 የተቃዋሚው መሪ ሪክ ማቻር በአሁኑ ወቅት በክስ ሂደት ላይ ቢሆኑም፣ የእሳቸው የፖለቲካ ንቅናቄ ሕገ-መንግሥታዊ መብቶቹን ሙሉ በሙሉ በመጠቀም በመንግሥት ተቋማት ውስጥ በንቃት እየተሳተፈ ይገኛል፡፡
🟠 26 ሰላማዊ ሰዎችን የገደለው የአየር ድብደባ መፈጸሙ ከተሰማ በኋላ፣ በሦስት የጆንግሌይ አውራጃዎች ሰላማዊ ሰዎች ተፈናቅለዋል፤ ይህም ለጥቃቱ “ሰላማዊ ሰዎችን ለጦርነት መከላከያ” እንዳያገለግሉ የተወሰደ የጥንቃቄ እርምጃ ነው፡፡
🟠 ሚኒስትሩ፣ በመጨረሻም ብሔራዊ መንግሥቱ በጎርጎሮሳዊያኑ 2026 ምርጫ ለማካሄድ እና የሰላም ስምምነቱን የደህንነት ዝግጅቶች ለማጠናቀቅ ያለውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጠዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X