ቤጂንግ በኢራን የውስጥ ጉዳይ የሚደረግን የውጭ ጣልቃ ገብነትን ታወግዛለች - የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ

ሰብስክራይብ

ቤጂንግ በኢራን የውስጥ ጉዳይ የሚደረግን የውጭ ጣልቃ ገብነትን ታወግዛለች - የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ

​የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማኦ ኒንግ በሰጡት መግለጫ፣ “እኛ ... በዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ውስጥ የኃይል አጠቃቀምን ወይም የኃይል ዛቻን አንደግፍም” ብለዋል።

​ቃል አቀባይዋ ይህንን ያሉት፣ ዶናልድ ትራምፕ የኢራን ተቃዋሚዎች ሰልፋቸውን እንዲቀጥሉና ስልጣን እንዲይዙ ካሳሰቡ በኋላ ሲሆን፤ ትራምፕ አክለውም “እርዳታ እየመጣላችሁ ነው” የሚል መልዕክትም አስተላልፈዋል።

​ማኦ ኒንግ ሁሉም ወገኖች በመካከለኛው ምስራቅ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ከፍተኛ ጥረት እንደሚያደርጉ ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0