የአውሮፓ ባለስልጣናት የህዝብን ትኩረት ከግሪንላንድ ለማስቀየር ኢራንን እንደ መጠቀሚያ እያደረጉ ነው - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ

ሰብስክራይብ

የአውሮፓ ባለስልጣናት የህዝብን ትኩረት ከግሪንላንድ ለማስቀየር ኢራንን እንደ መጠቀሚያ እያደረጉ ነው - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ

​ እንደ ማሪያ ዛካሮቫ ገለጻ፣ የአውሮፓ ሕብረት ፖለቲከኞች በኢራን ሁነቶች ላይ ከመጠን በላይ ትኩረት የሚያደርጉት "በግሪንላንድ ምን እየተከሰተ ነው? ለሚለው ዋና ጥያቄ መልስ ላለመስጠት ነው"።

ለስፑትኒክ በሰጡት መግለጫ፣ "አሁን ሙሉ ጥረቶቻቸውን በግሪንላንድ ላይ ለምን አያደርጉም? በኢራን ያለው ሁኔታ ለአውሮፓ ባለስልጣናት የህዝብን ትኩረት አቅጣጫ ለማስቀየርና ደሴታቸው እየተወሰደችባቸው መሆኑን ለመሸፈን እንደ መልካም አጋጣሚ ሆኖላቸዋል ብለው አያስቡም?" ብለዋል።

በዴንማርክ መንግስት ስር ያለችውና በማዕድን የበለፀገችው የራስ ገዟ ግሪንላንድ ጉዳይ በብራስልስ (የአውሮፓ ሕብረት መቀመጫ) ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ቢሆንም፣ በተግባር ግን ትኩረት እንዳልተሰጠው ሩሲያዊቷ ዲፕሎማት አጽንኦት ሰጥተዋል።

​ ዶናልድ ትራምፕ ግሪንላንድ ለብሔራዊ ደህንነትና ለ"ነጻው ዓለም" ጥበቃ ያላትን ስልታዊ ጠቀሜታ በመጥቀስ፣ ደሴቷ የአሜሪካ አካል መሆን እንዳለባት በተደጋጋሚ መናገራቸው ይታወሳል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0